Thursday 8 December 2016

ኢትዮጵያዊ የዐማራ ተጋድሎ

  ከጥቂት ወራት ወዲህ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረ ከሳቡ ወሳኝ ጉዳዮች ውስጥ የዐማራ መደራጀት ዋናው ሳይሆን አልቀረም ይህን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ ጽሑፎችና ንግግሮች ተደርገዋል ዐማራው እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነገድ መደራጀትና ራሱን ከተቀነባበረ ጥፋት ማዳን እንዳለበት የሚሞግቱ በርካቶች ናቸው አሳማኝ የመከራከሪያ ነጥቦችንም አንስተዋል በአንጻሩ ደግሞ ዐማራው በኢትዮጵያዊነት እንጅ በነገዱ መታገል መዘዙ ብዙ እንደሆነ ያስጠነቀቁ አሉ ከሁለቱም ወገኖች አንዳንዶች ነጥቦቻቸውን በምክንያት ወይም በመረጃና በማስረጃ መደገፍ ሲሳናቸው አፍ አውጥተው ሌሎች ጸሐፍትን ሲሳደቡና «ወያኔ ነህ» «ጸረ ዐማራ ነህ» እያሉ ሲያሸማቅቁ ታይተዋል ከነዚህ ከተሳዳቢዎችና ከአሸማቃቂዎች በስተቀር ለሌሎች ጸሐፍት ከፍ ያለ አክብሮትና ምሥጋና አቀርባለሁ መሠረት ያላቸው ውይይቶችና ክርክሮች ለሚደረገው ትግል ግልጽነትንና    መናበብን ይፈጥራሉና!      

Saturday 26 November 2016

Asrat Woldeyes & Ethiopian Politics

September 1997. I was in Bichena, the stronghold of the hero Belay Zeleke. My plan
was to reach at Addis Ababa University (AAU) for registration as a final year 
undergraduate student. Unfortunately, the scheduled bus failed to appear. Everyday 
around 6pm, we passengers were supposed to get registered afresh, hoping the bus 
could come the next day. We did registration six times, that is for six days. My 
money generously given by my relatives run real fast and I was in shock. But most 
worrisome was whether I could reach for the registration at AAU. Every passing day 
seriously touched my nerves. That time, no mobile, no Internet. It was real dark time.

Saturday 8 October 2016

የወቅቱ ፖለቲካዊ አሰላለፍና ፋይዳው

የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል እየሰፋና ቀጣይነቱን እያረጋገጠ ሲሄድ በውጭው ዓለም የሚገኙ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ባህርያቸውን ይበልጥ እየገለጡ መጥተዋል ግለሰብ ተኮር እንቅስቃሴዎች ወደ ድርጅት ወይም ማኀበር ወይም ኅብረት እየተለወጡ ነው ይበልጥ ትኩረት እየሳበ የመጣው ግን የድርጅቶቹ ብዛት ሳይሆን የተነሱበት ዓላማ ወይም ግብ ነው የአንዳንዶች የትግል ባህርይ ከተጠበቀው በአንፃሩ ሆኖ በመገኘቱ ጥቂት በማይባሉ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ቁጣና ግርምትን ፈጥሯል ይህን ተከትሎ ክርክሮችና ተግሳጾች በመገናኛ ብዙኃን እየወጡ ነው እኒህ አይነት እንቅስቃሴዎች ትግሉ ምን ያህል ሰላማዊና አንድነትን የተላበሰ እንደሚሆን ካሁኑ ግርታን ፈጥረዋል

Friday 9 September 2016

ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ!

በአገራችን በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ አሳሳቢ አጓጊም ሆኗል ፈጣሪ በኋላም ዓለም አቀፍና ብሄራዊ ሕግጋት የሰጧቸውን በፍጹም በነጻነት የመኖር መብታቸው እንዲከበርላቸው የጠየቁ ወገኖቻችን በመሰዋታቸው አካለ ስንኩላን በመሆናቸው የሲዖል አምሳያ በሆኑ እስር ቤቶች በመጋዛቸው መከራ ለበዛበት ስደት በመዳረጋቸው ባጠቃላይ እንደ ሰው በሰላም መኖር ባለመቻላቸው ሃዘናችን ወሰን የለውም  በአንጻሩ ደግሞ ለመኖር እየተደረገ ያለው አለመኖር ማለትም ትግል መንግስትን ክፉኛ ስላሸበረውና ደካማነቱን ከምንም ጊዜ በላይ አጉልቶ በማሳየቱ ሁኔታውን አጓጊ አድርጎታል ምንም ይሁን ምን ካሁን በኋላ መንግስትም ሕዝብም በነበሩበት የመግዛትና የመገዛት ሂደት ውስጥ መቀጠል አይችሉም ይህም አንዳች ለውጥ ሊመጣ እንዳለው አመላካች ስለሆነ ትግሉ ውጤታማ እየሆነ እንደመጣ ይገነዘቧል 


Friday 19 August 2016

ድር ቢያብር አንበሳ ያስር!

ታሪካዊ የለውጥ ጎዳና ለኢትዮጵያ በሚል ርዕስ በአገራችን እየተደረገ ያለው የሕዝብ ተቃውሞ አስፈላጊና አበረታች እንደሆነ ሞግቻለሁ የትግሉም ዓላማ እውነተኛና ዘላቂ ዴሞክራሲና ነጻነት ማስፈን እንደሆነም ከሕዝቡ መፈክሮች በመነሳት አትቻለሁ በተጨማሪም መንግስትና ደጋፊዎቹ ትግሉን በማካሄድ ላይ ያለው ሰፊው ሕዝብ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሃይማኖት ተቋማትና የመገናኛ ብዙኅን ይህን መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት ልዩና ላቅ ያለ አስተዋጽዖ ማድረግ እንዳለባቸው ጠቁሜያለሁ።ዝቡ የትግሉ ባለቤትና ኦዲተር ሆኖ አሥፈጻሚ አካል ወይም ልዩ ብሄራዊ ኮሚ ረጥ እንዳለበትም ለማሳየት ሞክሬ ነበር በመጨረሻም ኮሚቴው ለምንና እንዴት መመረጥ እንዳለበት ለመነሻ ያህል ጥቂት ነጥቦችን አንስቻለ በዚህ ጽሑፍ ደግሞ ይህ ለውጥ አስተባባሪ ኮሚቴ እንዴት እንደሚመረጥና የትግል መርሆቹና ስልቶቹ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ዘርዘር አድርጌ አቀርባለሁ    

Wednesday 10 August 2016

ታሪካዊ የለውጥ ጎዳና ለኢትዮጵያ

ኢትዮጵያዊያን እጅግ የተቀናጀ ያመረረና ቀጣይነትም ያለው የሚመስል ተቃውሞ በመንግስት ላይ እያካሄዱ ይገኛሉ። ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ እንደ ሰደድ እሳት ተቀጣጥሏል። የአዲስ አበባ የመስፋፋት እቅድና የመሬት ቅርምት እና የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ቢያነሳሱትም መሠረታዊ የሆኑ የመብትና የነጻነት እንዲሁም የፍትህ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው። ትግሉ በሰላማዊ ሰልፍ ተጀምሮ ሁለ ገብ የሆኑ ስልቶችን ወደ መጠቀም የተሸጋገረ ይመስላል። በመቶዎች የሚቆጠሩት ሰልፈኞች በመንግስት ታጣቂዎች ተገለዋል ቆስለዋል ታስረዋል። ከመንግስት በኩልም ቁጥራቸው ያልታወቀ ወገኖች ሞተዋል ቆስለዋል።  የታሰሩ ግን የሉም። ይህም ሁሉ መከራ ወርዶ ህዝቡ ለበለጠ ትግል ተነሳስቷል። እስካሁን የተከናወኑት ክስተቶች እንዲሁም ህዝቡ የሚያስተጋባቸው መፈክሮች በግልጽ እንደሚያሳዩት መንግስት በከፍተኛ ሁኔታ በህዝቡ ዘንድ  ተቀባይነትን እንዳጣ ለመረዳት ችሏል። ለመሆኑ ህዝባዊ ትግሉ አስፈላጊ ነውን?  

Thursday 30 June 2016

ማኅበረ ቅዱሳንና ፈታኞቹ የመጨረሻው ክፍል

መግቢያ
ስለወቅታዊ ጉዳዮች ለመጻፍ ተነሳስቼ ነበር ዳሩ ግን ከዚህ በፊት ስለማኅበረ ቅዱሳን ሁለት ተከታታይ ጽሑፎችን አቅርቤ ሦስተኛውን እንደምቀጥልበት ቃል መግባቴ ትዝ አለኝ ጥቂት አንባቢዎቼም «እስካሁን የጻፍካቸው ሁለቱ ጽሑፎች መግቢያ ናቸው ዋናውን አስከትልና እንተያያለን ብለውኝ እንደነበርም ትዝ አለኝ እናም በሥራ ምክንያት አቋርጨው የነበረውን የጀመርኩትን ጨርሼ እጅግ ወቅታዊ ወደሆኑ ጉዳዮች ማተኮር እንዳለብኝ ወስኜ ይህን የመጨረሻውን ክፍል አቀረብኩበዚህ አጋጣሚ አስተያየት የሰጣችሁኝን ሁሉ ከልብ እያመሰገንኩ ወደ ክፍል 3 ላምራ!  

Saturday 16 April 2016

ማኅበረ ቅዱሳንና አራቱ ፈታኞች ክፍል 2

ክፍል 1 ጽሑፌ ስለማኅበረ ቅዱሳን (ማቅ) መጻፍ ለምን እንዳስፈለገ ማኅበሩን እንዴት እንዳወቅኩትና ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ የማኅበሩን አመሰራረትና ዓላማ በጥቂቱ አቅርቤያለሁ በዚህ ክፍል ደግሞ ማቅን አብዝተው የሚፈትኑ አካላት እነማን እንደሆኑ በደረጃ ከነምክንያቶቻቸው አቀርባለሁ ይህ ጽሑፍ በክፍል 1 እንደተጠቀሰው ማቅንም ሆነ ሌላ አካልን ለመቃወምም ሆነ ለመደገፍ የተዘጋጀ አይደለም ያሉ እውነታዎችን ከግል እይታዬ በመነሳት በትንተና መልክ ለአንባቢ ማስገንዘብ እንጅበዚህ ጽሑፍ ምክንያት ሊነሱ የሚችሉ ውይይቶችና ሙግቶች በመጨረሻ የተሻለ ግንዛቤ እንዲመጣ ያደርጋሉ ብዬ አምናለሁ። ለጽሑፎቼ እንደ ግብዓት ያገለገሉኝ የግል ተሞክሮዬ የማቅ ገጸ ድርና እትሞች እንዲሁም ስለማቅ በተለያዩ ሚዲያዎች የተነሱ ዘገባዎች ናቸው    

Friday 8 April 2016

ማኅበረ ቅዱሳንና አራቱ ፈታኞች

ማኅበረ ቅዱሳንን በሚገባ ያወቅሁት የዛሬ 20 ዓመት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ግቢ የመጀመሪያ ድግሪ ተማሪ እያለሁ ነው ማኅበሩ ገና በእግሩ ለመቆም ጥረት በሚያደርግበት ወቅት  ማኅበረ ቅዱሳን (ከዚህ በኋላ ለማሳጠር ያህል ማቅ ወይም ማኅበሩ እያልኩ እጽፋለሁ) ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ በዩኒቨርስቲው ዋና ግቢ ያሉትን ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ በሚገኘው ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ባቋቋሙት ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ጋበዘ  ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጀምሮ በሰንበት ትምህርት ቤት ተሳታፊ ስለነበርኩና የዕውቀትም ጥማት ስለነበረብኝ የማኅበሩን ግብዣ በታላቅ ደስታ ተቀበልኩት

Friday 5 February 2016

ስደት ክርስትናና ኢትዮጵያዊነት ክፍል 2

ለተገፉት መቆም  

ክርስትና በግል የሚኖሩት ሕይወት አይደለም:: «እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት ለባልንጀራው እንጅ»  (ፊል 2: 4) እንዳለ ለሰው ልጅ ሁሉ ይልቁንስ ለኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን ደኅንነት ማሰብና የምንችለውን ማድረግ መንፈሳዊ ግዴታችን ነው:: በመካከለኛው ምሥራቅ በአፍሪካና በአውሮፓም ሳይቀር ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በመከራ ላይ ናቸው:: የሰው ልጅ የገጠመው ከባድ የተባለ መከራ ሁሉ የደረሰባቸው አሉ:: በየእስር ቤቶች የሚጉላሉና ጠያቂ ያጡ ብዙዎች ናቸው:: በደላሎችና በአሸባሪዎች እጅ የወደቁት ብዙ ናቸው:: የሰውነት ክፍሎቻቸው ለሽያጭ የቀረቡባቸው አሉ:: በሃይማኖታቸው ምክንያት መስዋዕትነትን የተቀበሉም አሉ:: ባጠቃላይ በሞትና በህይወት መካከል የሚገኙ ወገኖቻችን ብዙዎች ናቸው:: በአገራችን በኢትዮጵያም ቢሆን ያለአግባብ በእስር የሚማቅቁ የሚገደሉ የሚሳደዱ አሉ:: በረሃብ የሚሰቃየው ወገናችንም በሚሊዮን የሚቆጠር ሆኗል:: ሙስናና ዘረኝነት ህዝባችንን ተፈታትኗል:: ለእነዚህ ሁሉ ወገኖች ኢትዮጵያዊያን ሊደርሱላቸው ይገባል:: በጸሎት ከማሳሰብ ጀምሮ ገንዘብና አስፈላጊ ቁሳቁስ በመላክ እንታደጋቸው::

Friday 29 January 2016

ስደት ክርስትናና ኢትዮጵያዊነት

ስደት ለምን?

ስደት ከትውልድ አገር በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ወጥቶ በሌላ አገር ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ መኖርን ያመለክታል:: በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ስደተኞች አዳምና ሔዋን ናቸው:: ምንም እንኳን እግዚአብሔር ከምድር አፈር ቢፈጥራቸውም አገራቸው በምሥራቅ በኩል ባለች በኤዶም ገነት ይሆን ዘንድ ፈቃዱ ሆነ:: አዳም በተፈጠረ 40 ቀኑ ሔዋን በተፈጠረች 80 ቀኗ ኤዶም ገነት ገቡ:: በዚያም ሰባት ዓመት ከአንድ ወር 17 ቀን በደስታ ከኖሩ በኋላ ጠላት ዲያብሎስ በእባብ ተመስሎ አሳታቸው:: የታዛዥነት ምልክት የሆነችውን ያልተፈቀደላቸውን ዕፀ በለስን ስለበሉ እግዚአብሔር ከገነት አስወጣቸው:: በተፈጠሩባት ምድር በድካም እንዲኖሩ ተፈረደባቸው:: ስደት ወደ ምድር:: አዳምና ሔዋን እግዚአብሔርን በማሳዘናቸውና ገነትን በማጣታቸው ሐዘን ላይ እያሉ ክፉ ልብ የነበረው (1ዮሐ 3: 11 - 12) ልጃቸው ቃየን በቅናት ተነሳስቶ ወንድሙን አቤልን ገደለው:: በእግዚአብሔር አምሳያ የተፈጠረውን ሰውን በመግደል የመጀመሪያው ሰው ሆነ:: ከቤተሰቡና ከእግዚአብሔር ቁጣ የሚያመልጥ መስሎት ኖድ ወደተባለ አገር ተሰደደ:: እድሜ ልኩን ተቅበዝባዥ ሆነ:: ባጠቃላይ ሲታይ የዚህ ቤተሰብ አባላት ማለትም አዳም ሔዋንና ቃየን መራር ለሆነ ስደትና መከራ የተዳረጉት በራሳቸው ኃጢአት የተነሳ  ነው::

Who will Win: Fano or the Government?

  The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more   complicated than everyone’s expectation. ...