Thursday 26 September 2013

የማታ እንጀራ ይስጥህ!

አገር ቤት ያደገ ወይም የቆየ ሰው ብዙ አባባሎችንና ምርቃኖችን እድሜ ከጠገቡ (እድሜ ካስቆጠሩ) ሰዎች ይሰማል ይማራል:: ከነዚህም ውስጥ የማታ እንጀራ ይስጥህ የሚለው ምርቃት ቀልብን ይስባል:: ገና ነፍስ ሳላውቅ የዚህ አባባል ትርጉም አይገባኝም ነበር:: ትርጉሙን የመጠየቅም እድሉና አቅሙ አልነበረኝም:: ነገር ግን በ20ዎቹ የእድሜየ ክልል ሳለሁ አንድ የተባረከ ሰው ትርጉሙን ሲያብራራ ሰማሁት:: ሳልጠይቅ ያገኘሁት መልስ ነበር:: ከዚያ በኋላ ለአባባሉ ልዩ ክብር መስጠት ጀመርኩ:: 

Friday 13 September 2013

አዲስ ፕሬዚደንት በአዲስ ዓመት

ሰባት ዓመት ገደማ ነው:: ባህር ዳር ከተማ ፓፒረስ ሆቴል ሻይ ቡና እያልኩ በሆቴሉ የመዋኛ ቦታ ዙሪያ እንደትል የሚርመሰመሱ ህጻናትና አዋቂ ሰዎችን እመለከታለሁ:: በሰዎች ብዛትና በመዋኛ ቦታው ስፋት አለመመጣጠን እየተገረምኩ ሳለ ድንገት የጦር ወሬ የተሰማ ይመስል ህዝቡ ሁሉ መሯሯጥ ጀመረ:: የሆቴሉ ሥራ አሥኪያጅና ሌሎች ሠራተኞች ዋናተኞችንና ሌሎች ተስተናጋጆችን ማዋከብ ጀመሩ:: ሁሉም ሰው ሆቴሉን ባስቸኳይ ለቆ እንዲወጣ ይለማመጣሉም ያመናጭቃሉም::

Friday 6 September 2013

አዲስ ዓመት አዲስ ስብእና!

ኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ልትቀበል አምስት ቀናት ቀራታል:: 2006 ዓ.ም.:: በዚህ አዲስ ዓመት ሃገራችን ቢያንስ ዳጎስ ያለ ለውጥ ማየት ይኖርባታል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ:: ይህ ደግሞ  ምትሃትን ወይም ተአምርን አይፈልግም:: እያንዳንዳችን ድርሻችንን በሚገባ ከተወጣን ሊሳካ የሚችል ግብ ነው:: ከዚህ አኳያ በኔ እምነት ቀጥለው የተዘረዘሩትን ብንወጣ በአዲሱ ዓመት ቢያንስ ትክክለኛውን የለውጥ ጎዳና እንይዛለን:: ይህ ታላቅ ሃገራዊ ጎዳና የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን ቤትና ግቢ ነው:: ይህ እውነታ ተዘንግቶ ለውጥ ለማምጣት መሞከር የራስን ግቢ ሳያጸዱ ያካባቢን ንጽህና እጠብቃለሁ ብሎ  እንደማሰብ ነው::

Tuesday 3 September 2013

የትግራይ ህዝብ ሥጋትና የህወሓት ፖለቲካ

የትግራይ ህዝብ ከኢሕአዴግ መንግስት ምን ተጠቅሟል? የትግራይ ህዝብና መንግስት ምን አይነት ግንኙነት አላቸው? እነዚህንና ተያያዥ ጥያቄዎችን በተመለከተ አብርሃ በላይ ከመቀሌ አጥጋቢ መልስ ሰጥቷል:: አብርሃ እንደመነሻ ያደረገው ከአንድ የትግራይ ተወላጅ የቀረበለትን ጥያቄ ነው::  ጥያቄውም ይህ ነው:: “ኢህኣዴግን ትቃወማለህ፣ ግን ህዝብን ለለውጥ ኣነሳስተህ ከህወሓት የባሱ ፅንፈኛ የፖለቲካ ድርጅቶች ስልጣን ቢይዙስ ??? ስትቃወም ስለዉጤቱም ማሰብ ኣለብህ። በምትፅፋቸውን ነገሮች ለአዳንድ የትግራይ ጠላቶች መጋበርያ እየሆንክ ነው።”

Who will Win: Fano or the Government?

  The government's war for "disarmament" in the Amhara region has become much more   complicated than everyone’s expectation. ...